ማገልገል ክብር ነው!የአሽከርካሪ ተሽከርካሪ ፈቃድ ቁጥጥር ባለስልጣን በአዲስ አበባ ከተማ አስታዳደር ስር ያሉ አስፈፃሚ አካላትን እንደ አዲስ ለማዋቀር በወጣው አዋጅ 43/2007 መሰረት ተጠሪነቱ ለአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ሆኖ በከተማ አስተዳደር የሚገኙ የአሽከርካሪ ተሽከርካሪ ተቋማትን በማደራጀት፣ ክትትልና ቁጥጥር አግባብን በማጠናከር አፈፃፀማቸውን በማሳደግ የአገልግሎት አሰጣጡን ጥናትና ምርምር በማካሄድ ውጤታማ የአሽከርካሪ ተሸከርካሪ ቁጥጥር ብቃት ማረጋገጥ ዋነኛ የባለስልጣኑ ተልዕኮ እንዲኖረው ተደርጎ የተቋቋመ ሲሆን ባለስልጣን መስሪያ ቤቱም በአዋጁ የተሰጡትን ተግባራትና ሃላፊነቶች ተደራሽ እና ተገቢ በሆነ መልኩ ለመወጣት በማዕከል እና በአስራ ሁለት ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች ከ2008 ዓ/ም ጀምሮ እየሰጠ ያለ ሲሆን ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከተማ አስተዳደሩ በ2016 ዓ/ም ሪፎርም እንዲያደርጉ ከተመረጡ 16 ተቋማት መካከል አንዱ በመሆኑ የተሰጡትን ተግባርና ሃላፊነቶች በተሻለ መንገድ ለመወጣት እንዲያስችለው የሰው ሃይል እና የአደረጃጀት ለውጥ በማድረግ በአዲስ መልክ ተደራጅቷል፡፡ እኛም እናንተን ዝቅ ብለን ስናገለግል ታላቅ ደስታና ክብር ይሰማናል፡፡ ባለስልጣን መስሪያቤቱ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች በተቀመጡት ቅድመ ሁኔታዎችና ስታንዳርዶች ያለምንም ችግር የማግኘት መብት ያላችሁ ሲሆን በዚህ ሰነድ የተቀመጡትን አገልግሎቶች ለማግኘት ምንም እንቅፋት ቢገጥማችሁ ችግራችሁን ለመፍታትና ችግሩን የፈጠሩ አካላትን በአሰራርና በህግ አግባብ ለመጠየቅ ዝግጁ መሆናችንን እንዲሁም ሁልጊዜም እናንተን ለማገልገል በራችን ክፍት መሆኑን ልገልጽ እንወዳለሁ፡፡
በከተማችን ብቁ አሽከርካሪና ብቃቱ የተረጋገጠ ተሸከርካሪ ኢንዲኖር በማድረግ በ2023 ዓ.ም የሀገራችን ሞዴል አገልግሎት ሰጪ ተቋም ሆኖ ማየት ነው
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚገኙ የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ተቋማትን በማደራጀት፣ የክትትልና ድገፍ እንዱሁም የቁጥጥርና የግምገማ አግባብን በማጠናከር፣ አፈፃፀማቸዉን በማሳደግ፤ አገልግሎት አሰጣጡንና የመረጃ አያያዝ ስርዓትን በማዘመን እንዲሁም ጥናትና የዓሰራር ማሻሻያን በማካሄድ ዉጤታማ የአሽከርካሪና ተሸከርካሪ ፈቃድና ብቃት ማረጋገጥ ነዉ፡፡
1. ቅንነት (Integrity) 2. ግልፀኝነት (Transparency) 3. ተጠያቂነት (Accountability) 4. አለማዳላት (Imparciality) 5. ቅልጥፍናና ውጤታማነት (Efficiency & Effectiveness) 6. ቅንጅትና ትብብር (Integration and Collaboration)
1. የአሽከርካሪ ማሰልጠኛ ተቋማት ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ መስጠት . አግባብ ባለው ህግ መሰረት ተሽከርካሪዎችን ይመዘግባል፣ የስም ዝውውር፣ የእዳና እገዳ አገልገሎት ይሰጣል
2. ለአሽከርካሪ አሰልጣኞች ማስተማሪያ ፈቃድ መስጠት I. ለአሽከርካሪ አሰልጣኞች ማስተማሪያ ፈቃድ መስጠት II. ለአሽከርካሪ አሰልጣኞች ማስተማሪያ ፈቃድ ማደስ III. ለአሽከርካሪ አሰልጣኞች ማስተማሪያ ፈቃድ ለውጥ መስጠት
3. ለማሰልጠኛ ተቋማት የማለማመጃ ተሽከርካሪ ጭማሪና ቅያሪ ፈቃድ መስጠት I. የማሰልጠኛ ተቋማት ተመሳሳይ ካታጎሪ ጥያቄ ቅያሬ መስጠት II. የማሰልጠኛ ተቋማት ተመሳሳይ ያልሆነ ካታጎሪ ጥያቄ ቅያሬ መስጠት III. የማሰልጠኛ ተቋማት ተሽከርካሪ ጭማሬ መስጠት
4. በታክሲ አገልግሎት የተመዘገቡ ተሽከርካሪዎችን ለማሽከርከር የሚያስችለውን ስልጠና አገልግሎት መስጠት I. የታክሲ ልዩ ስልጠና ሰነድ ገቢ መቀበል II. የታክሲ ልዩ ስልጠና ሰነድ ወጪ ማድረግ
5. የእጩ አሽከርካሪዎች ምዝገባ አገልግሎት መስጠት I. የእጩ አሽከርካሪዎች ምዝገባ አገልግሎት II. የእጩ አሽከርካሪዎች ምዝገባ ሰነድ ማጣራትና የማረጋገጥ አገልግሎት
6. የእጩ አሽከርካሪዎች የምዘና ቀጠሮ መስጠት I. የእጩ አሽከርካሪዎች የንድፈ ሃሳብ የምዘና ቀጠሮ መስጠት II. የእጩ አሽከርካሪዎች የተግባር የምዘና ቀጠሮ መስጠት
1. የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ እድሳት አገልግሎት መስጠት 2. ወደ ውጪ ሃገር ለሚሄዱ አሽከርካሪዎች የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ትክክለኛነት ማረጋገጫ መስጠት (ኢንተርናሽናል) 3. የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ምትክ መስጠት 4. ከአዲስ አበባ ወደ ክልል ፋይል ዝውውር አገልግሎት መስጠት 5. የልዩነት ስልጠና ለሚወስዱ አሽከርካሪዎች መረጃዎችን መስጠት 6. በታክሲ አገልግሎት የተመዘገቡ ተሽከርካሪዎችን ለማሽከርከር የሚያስችለውን ብቃት ማረጋገጫ መስጠት 7. የንድፈ ሃሳብ ምዘና መስጠት 8. የንድፈ ሃሳብ ምዘና ለወደቁ ተፈታኞች ድጋሚ ቀጠሮ መስጠት 9. የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ እግድ ማንሳት 10. የአሽከርካሪ መረጃ መስጠት
The Driver's Vehicle Permit Control Authority under the Addis Ababa City Administration provides a range of services aimed at regulating and monitoring vehicle permits, ensuring safety, and maintaining compliance with transportation laws
Issuance of Driver's Licenses Vehicle Registration and Permits Inspection Services Permit Enforcement Data Management and Record Keeping Public Awareness and Training1. አሽከርካሪዎች 2. የተሽከርካሪ ባለንብረቶች 3. የአሽከርካሪ ማሰልጠኛ ተቋማት 4. የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ፈላጊዎች /እጩ አሽከርካሪዎች/ 5. የተሽከርካሪ ምርመራ ተቋማት 6. የተሽከርካሪ ጥገና ተቋማት 7. ባንኮችና ኢንሹራንሶች .
dlvca
dlvca
dlvca
dlvca
dlvca
dlvca
In General, the services provided by the Driver's Vehicle Permit Control Authority contribute significantly to Addis Ababa's transformation into a safer, more organized, and environmentally conscious urban center. These benefits align with the city's long-term goals of sustainability, economic development, and enhanced quality of life.
The Driver’s Vehicle Permit Control Authority in Addis Ababa offers several advantages to the city, contributing to its development, safety, and efficiency.
22 ወደ መገናኛ መንገድ መክሊት ህንፃ
info@dvlca.gov.et
0116672315/0116672329
Toll Free 7766
© 2025 Addis Ababa Driver and vehicle licensing and Control Autority. All rights reserved.